በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

መዝሙር 28

የይሖዋ ወዳጅ መሆን

የይሖዋ ወዳጅ መሆን

(መዝሙር 15)

  1. 1. ያንተ ወዳጅ ማን ነው?

    በድንኳንህ ’ሚያድረው?

    በደንብ የሚያውቅህ፣ የምታምነው፣

    ያንተ ወዳጅ ማን ነው?

    ቃልህን የሚወድ፣

    የሚታመንብህ፣

    ጥሩና ታማኝ የሆነ ሰው፣

    ሕይወቱን ’ሚሰጥህ።

  2. 2. ያንተ ወዳጅ ማን ነው?

    ዙፋንህ ’ሚቀርበው?

    ደስ የምትሰኝበትና

    በስም የምታውቀው?

    ስምህን ’ሚያወድስ፣

    ቃልህን ’ሚጠብቅ፣

    ሁሌም ሐቀኛ የሆነ ሰው፣

    ከመዋሸት ’ሚርቅ።

  3. 3. የሚያስጨንቀንን

    በጸሎት ስንነግርህ፣

    ’ሚያስፈልገንን ታሟላለህ፤

    ስቦናል ይህ ፍቅርህ።

    ሁሌም ያንተ ወዳጅ

    መሆን ያጓጓናል፤

    ከዚህ የሚበልጥ ወዳጅነት

    ከወዴት ይገኛል?

(በተጨማሪም መዝ. 139:1⁠ን እና 1 ጴጥ. 5:6, 7⁠ን ተመልከት።)